በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ የባህር ዳር ቴክኖሎጂ ኢንሰቲትዩት ከጣና በለስ የተቀናጀ የስኳር ልማት ፕሮጀክት ጋር በመተባበር የአካባቢውን ማህበረሰብ ከቦታቸው ሳይርቁ እንዲማሩ በማሰብ ጃዊ ከተማ ላይ በመጀመሪያ ዲግሪ በኮምፒዩተር ሳይንስ እና በ አውቶሞቲቪ እንጂነሪንግ እንዲሁም በሁለተኛ ዲግሪ በማኑፋክቸሪንግ እንጂነሪንግ ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር የጀመረ ሲሆን በቀጣይም በሌሎች የእንጂነሪንግ የስልጠና መስኮቸ አዲስ ተማሪዎቸን ተቀብሎ ማስተማር የሚጀምር መሆኑን በመከፈቻው ፕሮግራም ላይ ተገልጿል::