News page

የብሉ ናይል የውሃ ተቋምና የውሃና  ኢነርጂ ሚኒስቴር  በውሃ፣ ዘውሃ ዲፕሎማሲና ተግባቦት  መድረክ ጉባኤ አካሄደ

መስከረም 06/2015 ዓ/ም፤ [ባዳዩ] የብሉ ናይል የውሃ ተቋምና ኢነርጂ ማዕከል የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ካሉት አምስት የልህቀት ማዕከላት አንዱ መሆኑ ተገለፀ፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር የውሃ ዲፕሎማሲና ተግባቦት መማክርት መድረክ (WHDCF) በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበብ አዳራሽ አካሂዷል፡፡

በምክክር መድረኩ ላይ በመገኘት ለተሳታፊዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያቀረቡት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኘ ለተሳታፊዎች በአፍሪካ ከሚገኙ ጤናማና ውብ ከተማ አንዷ ወደ ሆነችዉ እና በዩኒስኮ የትምህርት ከተማ ተብላ ወደተመዘገበችዉ ባሕር ዳር ከተማ እንኳን በሰላም መጣችሁ ብለዋል፡፡

Pages